የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ካቢኔ 6ኛ ዓመት 1ኛ መደበኛ ስብሰባ በዛሬው ዕለት አካሄደ።
ካቢኔው በዛሬው ስብሰባው በቀረቡ አጀንዳዎች ላይ ተወያይቶ ውሳኔዎችን አስተላልፏል፡፡
በዚህ መሠረት፦
1- የማህበረሰብ አቀፍ ጤና መድህን ተጠቃሚዎች መዋጮን ለማሻሻል የቀረበ የውሳኔ ሀሳብ ተወያይቶ ተግባራዊ እንዲሆን አፅድቋል።
2- ሀገራዊ ፋይዳ ላላቸው ፕሮጀክቶች (ለሆቴል፣ ለሞልና አፓርትመንት፣ ኢንዱስትሪ፣ ለበጎ አድራጎት፣ መንግስታዊ ተቋማት እና የህክምና ተቋማት) የማስፋፍያና አዳዲስ የመሬት ጥያቄዎችን ለመመለስ የቀረበ የውሳኔ ሀሳብ ላይ ተወያይቶ ተፈፃሚ እንዲሆን አፅድቋል።
3- በከፊል በኮሪደር ለምተው፣ በከፊል ሳይለሙ የቆዩ አካባቢዎችን በተሟላ ሁኔታ ለማልማት የቀረበ የውሳኔ ሀሳብ ላይ ተወያይቶ ተግባራዊ እንዲሆን አፅድቋል።
Comments
ምንም አልተገኘም.
አስተያየቶችዎን ይተዉት.