የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ካቢኔ 6ኛ ዓመት...

image description
- ውስጥ Current Affairs    0

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ካቢኔ 6ኛ ዓመት 1ኛ መደበኛ ስብሰባ በዛሬው ዕለት አካሄደ።

ካቢኔው በዛሬው ስብሰባው በቀረቡ  አጀንዳዎች ላይ ተወያይቶ  ውሳኔዎችን  አስተላልፏል፡፡

በዚህ መሠረት፦ 

1- የማህበረሰብ አቀፍ ጤና መድህን ተጠቃሚዎች መዋጮን ለማሻሻል የቀረበ የውሳኔ ሀሳብ ተወያይቶ ተግባራዊ እንዲሆን አፅድቋል። 

2- ሀገራዊ ፋይዳ ላላቸው ፕሮጀክቶች (ለሆቴል፣ ለሞልና አፓርትመንት፣ ኢንዱስትሪ፣ ለበጎ አድራጎት፣ መንግስታዊ ተቋማት እና የህክምና ተቋማት) የማስፋፍያና አዳዲስ የመሬት ጥያቄዎችን ለመመለስ የቀረበ የውሳኔ ሀሳብ ላይ ተወያይቶ ተፈፃሚ እንዲሆን አፅድቋል። 

3- በከፊል በኮሪደር ለምተው፣ በከፊል ሳይለሙ የቆዩ አካባቢዎችን በተሟላ ሁኔታ ለማልማት የቀረበ የውሳኔ ሀሳብ ላይ ተወያይቶ ተግባራዊ እንዲሆን አፅድቋል።


Comments

ምንም አልተገኘም.

አስተያየቶችዎን ይተዉት.