በዓለም ባንክ የኢትዮጵያ፣ ኤርትራ፣ ሱዳን እና...

image description
- ውስጥ Current Affairs    0

በዓለም ባንክ የኢትዮጵያ፣ ኤርትራ፣ ሱዳን እና ደቡብ ሱዳን ዳይሬክተር ክብርት ማርያም ሳሊም ጋር የአዲስ አበባን የትራንስፖርት አገልግሎት ለማሻሻል በጋራ መስራት ላይ ፍሬያማ ውይይት አድርገናል።

በከተማ አስተዳደራችን የትራንስፖርት ዘርፉን ለማዘመን በተለይ E- mobility (የጭስ አልባ ትራንስፖርት) ተደራሽነትን  ለማስፋፋት እየሰራን ያለነውን ስራ ለማጠናከር እና በዘርፉ የተሰማሩ የግል ሴክተሮችንም ለመደገፍ ከዓለም ባንክ  ጋር በአጋርነት እና  በትብብር ለመስራት ከክብርት ከማርያም ሳሊም  ጋር  ተግባብተናል ።
 
ክብርት ማርያም ሳሊምን  እና የቴክኒካል ቡድናቸውን በራሴና  በከተማው ህዝብ ስም ከልብ አመሰግናለሁ ።
 
 ፈጣሪ ኢትዮጵያን እና ህዝቦቿን ይባርክ!


Comments

ምንም አልተገኘም.

አስተያየቶችዎን ይተዉት.