በዓለም ባንክ የኢትዮጵያ፣ ኤርትራ፣ ሱዳን እና ደቡብ ሱዳን ዳይሬክተር ክብርት ማርያም ሳሊም ጋር የአዲስ አበባን የትራንስፖርት አገልግሎት ለማሻሻል በጋራ መስራት ላይ ፍሬያማ ውይይት አድርገናል።
በከተማ አስተዳደራችን የትራንስፖርት ዘርፉን ለማዘመን በተለይ E- mobility (የጭስ አልባ ትራንስፖርት) ተደራሽነትን ለማስፋፋት እየሰራን ያለነውን ስራ ለማጠናከር እና በዘርፉ የተሰማሩ የግል ሴክተሮችንም ለመደገፍ ከዓለም ባንክ ጋር በአጋርነት እና በትብብር ለመስራት ከክብርት ከማርያም ሳሊም ጋር ተግባብተናል ።
ክብርት ማርያም ሳሊምን እና የቴክኒካል ቡድናቸውን በራሴና በከተማው ህዝብ ስም ከልብ አመሰግናለሁ ።
ፈጣሪ ኢትዮጵያን እና ህዝቦቿን ይባርክ!
Comments
ምንም አልተገኘም.
አስተያየቶችዎን ይተዉት.