"የአፍሪካ የህክምና ትምህርት ጉባኤ" ተሳታፊዎች በመዲናዋ የሚገኙ የቱሪዝም መዳረሻዎችንና ታሪካዊ ቦታዎች ጎበኙ።
ከ52 በላይ ሀገራትን ያሳተፈው "2ኛው የአፍሪካ የህክምና ትምህርት አህጉራዊ ጉባኤ" በአዲስ አበባ ተካሂዷል:: የጉባኤው ተሳታፊዎች በቆይታቸው፣ በአዲስ አበባ የሚገኙ የቱሪዝም መዳረሻዎችንና ታሪካዊ ስፍራዎችን ጎብኝተዋል::
ከቅርብ አመታት ወዲህ በርካታ አለም ዓቀፍ እና አህጉር ዓቀፍ ጉባኤዎችን በብቃት እያስተናገደች የምትገኘው አዲስ አበባ፣ በኮንፍረንስ ቱሪዝም እድገት መሠረታዊ ለውጥ እያስመዘገበች ትገኛለች::
የአዲስ አበባ ቱሪዝም ኮሚሽን፣ የተለያዩ ጉባኤ ተሳታፊዎች ከሚያካሂዱት ጉባኤ ጎን ለጎን፣ በመዲናዋ የሚገኙ የቱሪዝም መዳረሻዎችን እንዲጎበኙ በርካታ የማስተዋወቅ ስራዎችን እያከናወነ ይገኛል::
Comments
ምንም አልተገኘም.
አስተያየቶችዎን ይተዉት.