#የጠሚሩምላሾች
ሰላምና መረጋጋትን በተመለከት
“በኢትዮጵያ በተለያዩ አከባቢዎች የተፈጠሩ አለመረጋጋቶችን ለመፍታት መንግሥት ከ4000 በላይ የምክክር መድረኮችንና በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎችን በማሳተፍ በኢትዮጵያ ታሪክ ትልቁን የብሔራዊ መግባባት ምእራፍ ተሻግረናል። ባንዳዎችንና ጽንፈኞችን የምናሸንፈው በተጠናክረ ውይይት ብቻ ነው።”
ሀገራዊ ምክክርን በተመለከተ
“ይህንን ሰፊ ሀገራዊ እድል በመጠቀም፣ ካለፉት እሰጥ አገባዎች ወጥተን በሰለጠነ መንገድ መወያየት ይኖርብናል። በሕገ መንግሥቱ ውስጥ ያሉትን አወንታዊ እሴቶች ይዘን እንቀጥል፤ ማሻሻያ የሚያስፈልጋቸውን ነጥቦች ደግሞ ማንንም በማይጎዳ፣ የሁሉንም መብት በሚያከብርና አንድነታችንን በሚያጠናክር መልኩ እናሻሽላለን።ዋናው መገንዘብ ያለብን ነጥብ፦ አሁን የምንመክረው የአንድን ጊዜያዊ ገዥ ፓርቲ ስህተት ለማረም ብቻ አይደለም። ይልቁኑ ለዘመናት የተከማቹ ስር የሰደዱ ሀገራዊ ችግሮቻችንን በጋራ ጠረጴዛ ዙሪያ ፈትተን፣ ለአዲሲቷ ኢትዮጵያ የሚበጅ አዲስ ማህበራዊ ውል ለመፈረም ነው። ይህ ምክክር በመወያየት፣ በመነጋገርና በመተማመን እንዴት አብሮ መኖር ይቻላል ለሚለው ታሪካዊ ጥያቄ ዘላቂ ምላሽ የምንሰጥበት ብቸኛው መንገድ ነው!”
Comments
ምንም አልተገኘም.
አስተያየቶችዎን ይተዉት.