በ6ኛው የኢፌዴሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በ...

image description
- ውስጥ Current Affairs    0

በ6ኛው የኢፌዴሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በ5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 30ኛ መደበኛ ስብሰባ ለጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የተነሡ ጥያቄዎች፦

👉 የወደብ የኅልውናችን ጉዳይ ነው፤ የወደብና የባህር በር ጉዳይ ምን ደረጃ ላይ እንዳለ ቢገልጹልን?

👉 የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ሂደት በተያዘለት የጊዜ ሠሌዳ መሠረት ተጠናቅቆ የታለመለትን ሀገራዊ ዓላማ እንዲያሳካ መንግሥት በቀጣይ ምን ዓይነት የሎጂስቲክስ፣ ፖለቲካዊና ተቋማዊ ድጋፍ ያደርጋል?

👉 ተጀምረው ላልተጠናቀቁ እና ታቅደው ላልተጀመሩ ፕሮጀክቶች ምን የታሰበ ነገር አለ?

👉 አነስተኛ ገቢ ላላቸው እና ለመንግሥት ሠራተኞች የኑሮ ጫናን ለመቋቋም ምን ታስቧል፤ ከሚመሠረተው አዲሱ መንግሥት ምን እንጠብቅ?

👉 የተማሪዎች ምገባ ፕሮግራም የሰብዓዊ መብት ጉዳይ ስለሆነ ለሁሉም ክልሎች አስገዳጅ ሆኖ ቢቀርብ?

👉 የመንግሥት መዋቅር ተጠቅሞ በዜጎች ላይ ምዝበራ የሚፈጽሙ አካላት ላይ ገዥው ፓርቲ መዋቅሩን የማጽዳት እና ተጠያቂነትን የማስፈኑን ጉዳይ እንዴት ሊያስተካክለው አስቧል?

👉 ከፀጥታ አኳያ እየተሻሻሉ ያሉ ጉዳይ ቢኖርም፣ አሁንም አንዳንድ ቦታዎች ችግሮች አሉ፤ በዚህ ጉዳይ ላይ ምን መፍትሔ ለመስጠት ታስቧል?

👉 ከነዳጅ ጋር በተያያዘ፦ መንግሥት ለነዳጅ ድጎማ ቢያደርግም የነዳጅ ሽያጭ እና ስርጭት ከብልሹ አሠራር ሊድን አልቻለም። በዚህ ላይ መንግሥት የያዘው መፍትሔ ምንድን ነው?

👉 በትግራይ ክልል ዘላቂ ሰላም ለማረጋገጥ እና የትግራይ ሕዝብ የሰላም እንዲያገኝ በመንግሥት በኩል እየተደረገ ያለውን ጥረት ቢያሳውቁን?

👉 ሰላምን ወደ ዘላቂ መሠረት ለማሸጋገር ከምሁራን፣ ከፖለቲካ ፓርቲዎች እና ከህዝቡ ምን አይነት ንቁ ተሳትፎ ይጠበቃል?

👉 በትላልቅ ፕሮጀክቶች ምክንያት የሚነሡ ዜጎች መብት በአግባቡ እየተጠበቀ አይደለም የሚል ቅሬታ አለ። ፍትሐዊ የሆነ የካሳ አከፋፈል እና የመልካም አስተዳደር ችግሮችን ለመፍታት ምን ይደረጋል?

👉 የጠቅላይ ኦዲተር ሪፖርቶች ተደጋጋሚ የፋይናንስ ጉድለቶችን ቢያሳዩም፣ ተጠያቂነትን በማስፈን ረገድ ክፍተቶች አሉ። መንግሥት ተቋማትን ከሙስና እና ከመዝባሪ ኃይሎች ለማጽዳት ምን አዲስ አሠራር ይዘረጋል?


Comments

ምንም አልተገኘም.

አስተያየቶችዎን ይተዉት.