በፊና ኦሮሚያ የመስኖ ፕሮጀክቶች አማካኝነት በጎሞሌ ወረዳ ቦረና ዞን የመስኖ ግድቦች ግንባታ መጠናቀቅ፣ የአየር ንብረት ለውጥን በመቋቋም የውሃ መሠረተ ልማትን የማረጋገጥ ትልቅ ምዕራፍ መሆኑን የሚያሳይ ነው።
"በፊና ኦሮሚያ የመስኖ ፕሮጀክቶች አማካኝነት በጎሞሌ ወረዳ ቦረና ዞን የመስኖ ግድቦች ግንባታ መጠናቀቅ፣ የአየር ንብረት ለውጥን በመቋቋም የውሃ መሠረተ ልማትን የማረጋገጥ ትልቅ ምዕራፍ መሆኑን የሚያሳይ ነው። ይኸው እጅግ አስፈላጊ የሆነ መሠረተ ልማት በደሴ ጎራ ከ190 ሚሊዮን ኩቢክ ሜትር በላይ የሚሆን ከፍተኛ የውሃ ክምችት መያዝ የሚችል አቅም ያለው ሲሆን፣ አስተማማኝና ቀጣይነት ያለው የውሃ አቅርቦት እንዲኖር ያደርጋል። በተጨማሪም ፕሮጀክቶቹ ከ14,500 ሄክታር በላይ የሚሆን የግብርና መሬትን በመስኖ የማልማት አቅም ያለው በመሆኑ፣ እያንዳንዱን ቤተሰብ በቀጥታ ለመደገፍ፣ የምግብ ምርትን ለማጠናከር እና ለከብቶች የሚሆን የውሃ ሀብትን በበቂ ሁኔታ ለማረጋገጥ ያስችላሉ"።
ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ(ዶ/ር)
Comments
ምንም አልተገኘም.
አስተያየቶችዎን ይተዉት.