በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) እና ከ...

image description
- ውስጥ Current Affairs    0

በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) እና ከንቲባ አዳነች አቤቤ ተመርቆ ለአገልግሎት ክፍት የተደረገው የላፍቶ ሆስፒታል በውስጡ ከያዛቸው በሰው ሠራሽ አስተውሎት የሚደገፉ እጅግ የረቀቁ መሣሪያዎች መካከል፦

👉 የቅድመና ድህረ ካንሰር ምርመራ ማሽን፦ በምሥራቅ አፍሪካ የመጀመሪያው የሆነ ሰው ሠራሽ አስተውሎት የተገጠመለትና የ2026 ምርት የሆነ የመጨረሻው ዲጂታል ቴክኖሎጂ 

👉 በኢትዮጵያ የመጀመሪያ የሆነው የሂሊየም ትነትን ሙሉ በሙሉ የሚያስቀር መሣሪያ

👉 ከአንድ የልብ ትርታ ባነሰ ጊዜ ሙሉ ምርመራ ማድረግ የሚችል ፈጣን የምርመራ ቴክኖሎጂ

👉 የልብና የደም ሥር ላቦራቶሪ፦ በቀጭን የደም ሥር በመግባት የልብና የአንጎል ደም ሥር ችግሮችን በአጭር ጊዜ ለይቶ የሚያክም የዘመኑ የመጨረሻ ጥበብ

👉 የጡት ካንሰርን በቅድሚያ ለመመርመርና በሁሉም አቅጣጫ የናሙና ምርመራ ለመውሰድ የሚያስችል የረቀቀ መሣሪያ

👉 ሙሉ በሙሉ ከሰው እጅ ንክኪ ነጻ የሆነ የሰውን ስህተት በማስቀረት ፈጣንና ጥራቱን የጠበቀ ውጤት የሚሰጥ በሀገራችን የመጀመሪያው የላቦራቶሪ ሥርዓት 

👉 ዘመኑ የደረሰበት የመጨረሻው የቴክኖሎጂ ውጤት የሆኑ የአልትራሳውንድ እና የዲጂታል ማሽኖች 

👉 በሰዓት 80 ሜትር ኩብ ኦክስጂን የማምረት አቅም ያለውና የሜዲካል ጋዝ ማምረቻ ፕላንት

👉 በብዙ ሆስፒታሎች የሚያጋጥሙ የኢንፌክሽን ችግርን ለማስቀረት የሆስፒታሉ ግድግዳዎችና ወለሎች ባክቴሪያን ሙሉ በሙሉ በሚከላከል ቁስ የተገነቡ ናቸው

👉 የማይቋረጥና ዘላቂ አገልግሎት ለመስጠት ሲባል የራሱ የውሃ ጉድጓድና የፍሳሽ ማጣሪያ ፕላንት የተገጠመለት 

👉 ደረጃውን የጠበቀ 18 ዘመናዊ አስከሬን ለረጅም ጊዜ ማቆየት የሚያስችል ማቀዝቀዣን ጨምሮ በርካታ የህክምና ቴክኖሎጂዎችን ያካተተ ነው


Comments

ምንም አልተገኘም.

አስተያየቶችዎን ይተዉት.