በአዲስ አበባ ከተማ የጤና አገልግሎት ላይ የተጨመረ ትልቅ እመርታ!
የላፍቶ ሆስፒታል ግንባታ ተጠናቆ አገልግሎት መስጠት መጀመሩ በኢትዮጵያ የጤና አገልግሎት ዘርፍ ውስጥ ትልቅ ምዕራፍ ነው። ሆስፒታሉ አዲስ አበባን የህክምና ቱሪዝም ማዕከል ለማድረግ የተቀመጠውን ሀገራዊ ግብ ከመደገፉም በላይ ለህክምና ወደ ውጭ ሀገር የሚወጣውን የውጭ ምንዛሬ ለመቀነስ ከፍተኛ አስተዋፅዖ ይኖረዋል።
የተቋሙ አሁናዊ አቅም እና ርዕይ:-
በ5.4 ሄክታር መሬት ላይ ያረፈው ግዙፉ ሆስፒታል 17 ዘመናዊ ህንጻዎችንና 500 አልጋዎችን ይዟል። ተቋሙ የተገነባው የኢትዮጵያን የህክምና አቅም ለማጠናከር፣ የላቁ የህክምና አገልግሎቶች ተደራሽነትን ለማስፋት እና የልዩ ህክምና መዳረሻ እንድትሆን የተጀመረውን ጥረት ለመደገፍ ነው።
የላቀ የህክምና ቴክኖሎጂ:-
ሆስፒታሉ በሰው ሰራሽ አስተውሎት የታገዘ የዲጂታል የቅድመ ካንሰር እና ድህረ ካንሰር የምርመራ ማሽን ጨምሮ የሚከተሉትን ዘመናዊ
ህክምና ቴክኖሎጂዎች አካቷል፦
• ባለ 3-ቴስላ ኤም.አር.አይ (3-Tesla MRI) ማሽን
• ባለ 640-ስላይስ ሲቲ ስካን (640-slice CT scan)
• በድምጽ የሚታዘዝ የካቴተራይዜሽን ላብራቶሪ (Cath Lab)
• የ3ዲ (3D) ማሞግራፊ መሳሪያ
• የሮቦቲክስ ላብራቶሪ (TLA) መሳሪያ፤
እነዚህ ቴክኖሎጂዎች በሀገር ውስጥ ውስብስብ የሆኑ የጤና እክሎችን የመመርመር እና የማከም አቅምን በእጅጉ ያሻሽላሉ ተብሎ ይጠበቃል።
A MAJOR STEP FORWARD FOR HEALTHCARE SERVICES IN ADDIS ABABA
The completion of Lafto Hospital marks an important milestone in Ethiopia’s healthcare sector. The hospital is expected to support the country’s broader goal of positioning Addis Ababa as a center for medical tourism while helping reduce the foreign currency spent on medical treatment abroad.
Facility Scale and Vision:-
Built on 5.4 hectares of land, the hospital consists of 17 modern buildings and 500 beds. The facility was developed to strengthen Ethiopia’s healthcare capacity, expand access to advanced medical services, and support the country’s ambition to become a destination for specialized healthcare in East Africa.
Advanced Medical Technology:-
The hospital includes an AI-assisted digital PET scan system, alongside a range of advanced medical technologies, including:
- A 3-Tesla MRI system
- A 640-slice CT scan
- A voice-controlled Cath Lab
- 3D Mammography equipment
- Robotics Laboratory (TLA) equipment
These technologies are expected to improve the diagnosis and treatment of complex medical conditions within the country.
#PMOEthiopia #EthiopiaDelivers
Comments
ምንም አልተገኘም.
አስተያየቶችዎን ይተዉት.