በ2015 በከተማችን 11 ብቻ የነበረዉ የህዝብ የሕፃናት ማቆያን በ2018 ወደ 1100 በማሳደግ የምግብ ፣ የህክምና፣ የስነ ልቦና የእንክብካቤ አገልግሎት በነፃ እየሰጠን ነው።
በተጨማሪም በ2015 በከተማችን 20 ብቻ የነበረዉን የልጆች መጫወቻ በ2018 ወደ 5000 በማሳደግ ልጆች ቦርቀዉ የሚያድጉበት አካባቢን መፍጠር ችለናል።
እየሰራናቸው ባሉት ስራዎች በእድገት ወደ ኋላ የቀሩ ህጻናት መጠን በ2015 መርሃ ግብሩን ስንጀምር ከነበረበት 13% ወደ 10% ዝቅ ማድረግ የቻልን ሲሆን የአንደኛ ደረጃ ትምህርት ዝግጅታቸውም ከነበረበት 49% ወደ 90% ከፍ ማድረግ ተችሏል።
ከንቲባ አዳነች አቤቤ
Comments
ምንም አልተገኘም.
አስተያየቶችዎን ይተዉት.