ቃል በተግባር ፤ ሳይውል ሳያድር!
ተንቀሳቃሽ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎታችን በዛሬው ዕለት እየተዘዋወረ ወደህዝቡ ደጅ አገልግሎት ማድረሱን ጀምሯል።
አውተቡስ ላይ የተሰራዉ ተንቀሳቃሽ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎታችን መመረቁን ባበሰርን ማግስት፣ በንፉስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ-ከተማ በተለምዶ “ጀርመን አደባባይ” አካባቢ አገልግሎት ሲሰጥ ውሏል። ነገም ቀጥሎ በለሚ ኩራ ክፍለ-ከተማ አዲስ ኢንተርናሽናል ኮንቬንሽን አካባቢ አገልግሎቱን መስጠቱን ይቀጥላል።
አዲስ አበባን ወደ ስማርት ከተማነት የማዘመን ጉዞ ቀጥሏል!!
ፈጣሪ ኢትዮጵያን እና ህዝቦቿን ይባርክ!
ከንቲባ አዳነች አቤቤ
Comments
ምንም አልተገኘም.
አስተያየቶችዎን ይተዉት.