የአዲስ ከተማ ክ/ከተማ አስተዳደር የትንሳኤ በዓ...

image description
- ውስጥ Current Affairs    0

የአዲስ ከተማ ክ/ከተማ አስተዳደር የትንሳኤ በዓልን በአሙዲ የምገባ ማዕከል ከሚገኙ አረጋውያንና አቅመ ደካማ ዜጎች ጋር አከበረ፡፡

በእለቱ መልዕክት ያስተላለፉት በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሃብት ልማት ቢሮ ሃላፊ ዶ/ር ጀማሉ ጀንበር መንግስት በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ያሉ ወገኖቻችንን ልዩ ፍቅርና እንክብካቤ መስጠት ተገቢ መሆኑን ስለሚያምን በዓሉን ተደስታችሁ እንድታሳልፉ ታስቦ የተዘጋጀ ፕሮግራም ነው ብለዋል::

የአዲስ ከተማ ክ/ ከተማ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ታረቀኝ ወርቅነህ በበኩላቸው መንግስት ሰው ተኮር የሆኑ በርካታ እቅዶችን ነድፎ እየሰራ መሆኑን ጠቅሰው በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ለሚገኙ ዜጎች ፍቅርና እንክብካቤ ከመስጠት በተጨማሪ በዘላቂነት የሚቋቋሙበትን አግባብ ለመፍጠር እየተሰራ ይገኛል ሲሉ ተናግረዋል ::

የበዓሉ ታዳሚዎች በበኩላቸው በዓሉን በደስታ እንድናሳልፍ ይህን የመሰለ ደማቅ ፕሮግራም በመዘጋጀቱ እናመሰግናለን ሲሉ ተናግረዋል ::


Comments

ምንም አልተገኘም.

አስተያየቶችዎን ይተዉት.