የትንሳኤ በዓልን ስናከብር እርስ በራስ በመረዳዳ...

image description
- ውስጥ Current Affairs    0

የትንሳኤ በዓልን ስናከብር እርስ በራስ በመረዳዳት እና አቅመ ደካሞችን በመደገፍ ሊሆን እንደሚገባ የአዲስ አበባ ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ቡዜና አልከድር ተናገሩ!

የትንሳኤ በዓልን ምክንያት በማድረግ በአብርሆት ቤተ መጻህፍት አቅመ ደካማ አረጋውያንን ጾም የማስፈሰክ መርሃ ግብር ተካሂዷል።

በመርሃ ግብሩ ላይ በመገኘት ማዕድ ያጋሩት የአዲስ አበባ ምክር ቤት አፈ ጉባኤ እና የአብርሆት ቤተ መጻህፍት ቦርድ ሰብሳቢ ወ/ሮ ቡዜና አልከድር የጾሙን ወቅት በጸሎት ያሳለፉ አረጋውያን በትንሳኤ እለት በትውፊቱ መሰረት በሌሊት የማስፈሰክ መርሃ ግብር በአብርሆት ቤተ መጻህፍት ባለፉት አመታት ሲካሄደ መቆየቱን አስታውሰው ይህን መሰሉ በዓልን አብሮ የማክበር መርሃ ግብር ሊስፋፋ እና ሊጠናከር የሚገባው ነው ብለዋል።

ህብረተሰቡ በዓልን ሲያከብር በአከባቢው ያሉ አቅመ ደካሞችንና ለተለያዩ ማህበራዊ ችግሮች የተጋለጡ ወገኖችን በማሰብ እርስ በእርስ በመረዳዳት እና በመደጋገፍ ሊሆን እንደሚገባም ነው አፈ ጉባኤዋ የተናገሩት።


Comments

ምንም አልተገኘም.

አስተያየቶችዎን ይተዉት.