አንገት የሚያስደፉ ታሪኮቻችንን ቀልብሰን ፤ዛሬ ለዓለም ችለን መለወጣችንን በማሳየት ለአፍሪካ ኩራት ሆነን ትልቅ እንደ ነበርን፤ትልቅም ሆነን፤ታላቅነታችንን እያስቀጠልን እንገኛለን፡፡
ለዚህ ደግሞ መጋቢት 24 ቀን 2010 ዓ.ም አዳዲስ እሳቤዎች የተፀነሱበት፤በእነዚህ እሳቤዎች የ 8 ዓመታት ጉዞ ፖለቲካዊ፤ኢኮኖሚያዊ እና ማህበራዊ ስብራቶችን በመጠገን ሃገርን ህዝብን እና ታሪክን የሚመጥኑ የለዉጥ ትሩፋቶች በተጨባጭ የተመዘገቡበት መሆኑ ነዉ፡፡
በብዙ ዉጣ-ዉረዶች እና መስዕዋትነት የሀገር ሉዓላዊነትን በማፅናት እና በዉይይት የዳበረ የሃሳብ የበላይነት በማክበር በዲሞክራሲያዊ የምርጫ ስርዓት ለህዝብ ድምፅ ክብር በመስጠት ህዝቡ በራሱ ዳኛ እና ወሳኝ ሆኖ በዘመነ አስተሳሰብ እና በሰለጠነ መንገድ ጠንካራ ሃገረ-መንግስት በመገንባት ረገድ ተስፋ ሰጪ የፖለቲካ ስርዓት በመዘርጋት ኋላ-ቀር የፖለቲካ ባህል እና አስተሳሰቦች መቀልበስ ተችሏል፡፡
የወል ትርክቶቻችንን በጋራ በማፅናት እና ህብረ-ብሄራዊ አንድነታችንን በማስጠበቅ፤ለዜጎች እኩል ክብር በመስጠት፤ በአካል እና በአእምሮ የታነፀ እንዲሁም በማንነቱ እና በሃገሩ የሚኮራ ትዉልድ በመገንባት የሚታፈርባት ሳይሆን የሚኮራባት ከተማ እና ሃገር የፈጠርንበት ሌላዉ ማህበራዊ ስብራታችንን የጠገንበት የለዉጥ ትሩፋታችን ነዉ፡፡
ለአዋረደን ድህነት እጅ ላንሰጥ፤በእጅ አዙር ፖሊሲ እና እርዳታ ላንገዛ ሃገር በቀል የኢኮኖሚ ፖሊሲ ሪፎርም በመቅረፅና ወደ መሬት በማዉረድ በራሳችን ሃብት፤ፀጋ እና እዉቀት ላይ እሴት በመጨመር እንዲሁም ትናንት ያልተጠቀምንበት እና ያለ አግባብ ሲመዘበር የነበረዉ የሃገር ሃብት ዛሬ ለሃገር ልማትና ለትዉልድ ግንባታ በማዋል፤ኋላ-ቀር የስራ ባህላችንን በ24/7 በመቀየር፤ በአፍሪካ ትልቅ ኢኮኖሚ ከገነቡ ሃገራት ተርታ ለመሰለፍ የቻልንበት ኢኮኖሚያዊ ስብራትን የጠገንበት የለዉጥ መሰረት ነዉ፡፤
በአጠቃላይ ቁርጠኝነትንና ፅናትን የተላበሰ ዉሳኔ ሰጪ አመራር እና ለፈጣን እድገትና ለዉጥ የተነሳሳ እና የሚታትር ጀግና ህዝብ ይዘን ዛሬ በመዲናችን ሆነ እንደ ሃገር በሁለተናዊ ዘርፉ ያስመዘገብናቸዉ ድሎች ከተማችን ብቻ ሳትሆን ዓለም ተደምሞ የሚመሰክረዉ ሃቅ ለመሆን በቅቷል።
ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች
https://linktr.ee/addisababacommunication
Comments
ምንም አልተገኘም.
አስተያየቶችዎን ይተዉት.