ከአዲስ አበባ የግብር አሰባሰብና የገቢዎች አገል...

image description
- ውስጥ Current Affairs    0

ከአዲስ አበባ የግብር አሰባሰብና የገቢዎች አገልግሎት አሰጣጥ ጋር በተያያዘ ለሚኖር ማንኛዉም አይነት ቅሬታ መፍታት የሚያስችል አዲስ አሰራር በከንቲባ ፅ/ቤት ስር ተዋቅሯል ።

በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የገቢዎች ቢሮ ስር የተዘረጋዉ የቅሬታ አፈታት ስርዓት እንደተጠበቀ ሆኖ  በዛ ያልረካ ግብር ከፋይ ከንቲባ ፅ/ቤት ማንኛዉንም አይነት ከገቢ አሰባሰብ ፣ ከሰራተኞች ስነምግባር እና አገልግሎት አሰጣጥ ጋር የሚነሱ የግብር ከፋዮች ቅሬታዎችን ለመፍታት ዘወትር ሐሙስ ኃላፊዎች በተገኙበት የሚደመጥ እና ተጣርቶ ምላሽ የሚሰጥበትን አሰራር ዘርግቷል ።

ሁልጊዜም የአገልግሎት አሰጣጡን ለማሻሻል የሚተጋዉ እና ህዝብን አዳምጦ ምላሽ መስጠትን የትኩረት ማእከሉ ያደረገዉ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በከንቲባ ፅ/ቤት በሚስጥር ጥቆማ የሚሰጥበትን ነፃ የጥሪ ማእከል 9977 ፣ የሚስጥር ሳጥንን ጨምሮ  በተጨባጭ ቅሬታዉን በአካል ለበላይ አመራር ማቅረብ የሚችልበትን አሰራር የፊታችን ሐሙስ ጀምሮ ወደ ተግባር ይገባል ።

በመሆኑም ከመጪዉ ሐሙስ ህዳር 25/2018 ጀምሮ ጠዋት ከ 2 ሰአት እስከ 7 ሰአት ድረስ  ከገቢዎች ጋር ብቻ የተያያዘን ቅሬታ አመራሩ ተቀብሎ የሚስተናግድ መሆኑን በመረዳት በከንቲባ ፅ/ቤት ተጨባጭ ቅሬታ ያላችሁ ማቅረብ የምትችሉ መሆኑን የከተማዉ አስተዳደር ያሳዉቃል ።

አስተዳደራችን ለቀልጣፋ እና ፍትኃዊ አገልግሎት ይተጋል !


Comments

ምንም አልተገኘም.

አስተያየቶችዎን ይተዉት.