በሰውስራሽ አስተውሎት ዘርፍ ለመሰማራት ሃሳብ ፣...

image description
- ውስጥ Current Affairs    0

በሰውስራሽ አስተውሎት ዘርፍ ለመሰማራት ሃሳብ ፣ ፍላጎት ኖሯችሁ በተለያየ ምክንያት እድሉን ያላገኛችሁ የከተማችን ታዳጊዎች ፣ ወጣቶች በተመቻቸዉ የነፃ እድል እንድትጠቀሙ ጥሪዬን አቀርባለሁ፡-ከንቲባ አዳነች አቤቤ

ለኢትዮዽያዊያን የኩራት ምንጭ እንዲሆን ተደርጎ የተገነባዉን የኢትዮዽያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ዋና መስሪያ ቤትን የጎበኙት ከንቲባ አዳነች አቤቤ ባለፉት የለውጥ አመታት በአገራችን ከታዩ የማድረግ አቅሞች መካከል አንዱ የሁሉም ፣ በሁሉም የሆነችዉ የአዲሷን ኢትዮዽያ ተልዕኮ መሸከም የሚያስችሉ ተቋማትን መገንባት ነዉ ብለዋል።

የተቋማት ግንባታ ማሳያው ደግሞ የኢትዮዽያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት እንዱ ነው ። አጠቃላይ በተቋሙ የተመለከትነዉ ሁሉ እጅግ አስደናቂ ነዉ።

በዚህ የዉድድር አለም እንደ አገር ሉአላዊነትን አስጠብቆ ተወዳዳሪ ሆኖ ለመቆየት በየትኛዉም መስፈርት የሰዉ ሰራሽ አስተዉሎት አቅምን ማሳደግ ያስፈልጋል ።

ይህንን እዉነታ ከአመታት በፊት አስቀድሞ በመረዳት ለዚህም አገራዊ ተልዕኮን በብቃት የሚያሳካ እና በአለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ አቅም ያለዉ ተቋም በአጠረ ጊዜ እዉን እንዲሆን ላደረጉት ለክቡር ጠቅላይ ሚኒስትራችን ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ በከተማ አስተዳደሩ ስም ምስጋና አቅርበዋል።

ለመላዉ የኢትዮጵያ አርተፊሻል ኢንተሊጀንስ ኢንስቲትዩት አመራሮችና ባለሙያዎች እንኳን ደስ አላችሁ ብለዋል።

ከንቲባ አዳነች አቤቤ በዘርፉ ለመሰማራት ሀሳብ ፣ ፍላጎት እያላችሁ በተለያየ ምክንያት እድሉን ያላገኛችሁ የከተማችን ታዳጊዎች ፣ ወጣቶች ተቋሙ ባመቻቸዉ የነፃ እድል እንድትጠቀሙ ጥሪ አስተላልፈዋል ።


Comments

ምንም አልተገኘም.

አስተያየቶችዎን ይተዉት.