የዘንድሮውን ዘመን ስናበቃ የመንግሥት አገልግሎት...

image description
- ውስጥ Current Affairs    0

የዘንድሮውን ዘመን ስናበቃ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥ ሥርዓቱን የጠበቀ እና ቀልጣፋ መሆኑን ለማረጋገጥ የነበረን ቁርጠኝነት እንደቀጠለ ነው።

መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ከፌደራል አገልግሎቶች ወደ ክልሎች እና ከተማ አስተዳደሮች እየተስፋፋ ይገኛል። በአዲሱ አመት ዋዜማ በአስራ ሶስት ተቋማት አንድ መቶ ሰባት የከተማ አስተዳደር አገልግሎቶችን የሚሰጠውን የአዲስ መሶብ የአንድ ማዕከል ተመልክተናል። ይኽ አገልግሎት አሰጣጥን የመልካም አስተዳደር የድንጋይ ማዕዘን የማድረግ እና ዜጎች ወቅቱን የጠበቀ፣ ግልጽ እና ተደራሽ አገልግሎት የማረጋገጥ ቁርጠኝነታችንን የሚያንፀባርቅ ነው።

በአዲሱ አመት ገና ብዙ ማዕከላት ይኖሩናል። በድጋሚ መልካም አዲስ አመት።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)


Comments

ምንም አልተገኘም.

አስተያየቶችዎን ይተዉት.