ማምሻዉን የምዕራቧ ኮከብ በሆነችው በቤኒሻንጉል...

image description
- ውስጥ Current Affairs    0

ማምሻዉን የምዕራቧ ኮከብ በሆነችው በቤኒሻንጉል አሶሳ ከተማ ከወንድሜ ርዕሰ መስተዳድር ክቡር አሻድሊ ሀሰን ጋር በመሆን የአረንጓዴ አሻራችንን አኑረናል ::

በአሶሳ ከተማ "ሀለዋ የአግሮ ኢንዱስትሪ" መንደር በ60 ሄክታር ላይ ያረፈውን የሌማት ቱሩፍት የሆነውን የዶሮ ፣ የእንቁላል እና የወተት ተዋፅኦ በቀላል መንገድ በማልማትና የአካባቢ ሀብትን በመጠቅሞ እንዴት ምርታማነትን መጨመር እንደሚቻል ተዘዋውረን ጎብኝተናል::

አዲስ አባባ ከክልሎች ጋር የምርት አቅርቦት  ትስስር በመፍጠር ምርትን ወደ ከተማዋ እንዲገባ እየሰራች ትገኛለች በቀጣይም በኮሪደር ልማት የተሰሩትን ስራዎች ልምድ ልዉዉጥም የምናደርግ ይሆናል።

ስለ ተደረገልን ደማቅ አቀባበል እናአመሰግናለን !

ፈጣሪ ኢትዮጵያንና ህዝቦቿን ይባርክ !

ከንቲባ አዳነች አቤቤ

ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች
  https://linktr.ee/addisababacommunication


Comments

ምንም አልተገኘም.

አስተያየቶችዎን ይተዉት.