
የአዲስ አበባ ከተማ የ2018 ዓ.ም አጠቃላይ በጀት 350 .13 ቢሊየን ብር ሲሆን ከባለፈው ዓመት ጋር ሲነጻጸር የ108 ቢሊዮን ብር ወይም የ45 በመቶ ብልጫ አሳይቷል::በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የፋይናስ ቢሮ ሃላፊ አቶ አብዱልቃድር ሬድዋን
በ2018 በጀት ዓመት ከተያዘው በጀት 350.13 ቢሊየን ውስጥ ለመደበኛ በጀት ወጪዎች 100.1ቢሊዮን እና ለካፒታል ወጪዎች 249.9 ቢሊዮን ተብጅቷል::
ከዘንድሮው አጠቃላይ በጀት 343 ቢሊየን ብሩ ከሀገር ውስጥ ገቢ የሚሰበሰብ ሲሆን ከታክስ ገቢ 238 .93 ቢሊየን ብር ፣ ከማዘጋጃ ቤታዊ ገቢ 56 ቢሊየን ብር፣ ታክስ ካልሆኑ ገቢዎች 46 ቢሊየን ብር፣ ከመንገድ ፈንድ ጽህፈት ቤት 1 ነጥብ 8 ቢሊየን ብር እና ከውጭ እርዳታና ብድር ደግሞ 6 . 9 ቢሊየን ብር ይገኛል ተብሎ ታቅዷል።
Comments
ምንም አልተገኘም.
አስተያየቶችዎን ይተዉት.