የረዳን ፈጣሪ ይመስገን !! እንኳን ደስ አላችሁ...

image description
- ውስጥ Current Affairs    0

የረዳን ፈጣሪ ይመስገን !! እንኳን ደስ አላችሁ!!

ዛሬ በመዲናችን 31.5 ኪሎ ሜትር ርዝመት ያላቸዉ 13 የመንገድ ፕሮጀክቶችን እና 8 ድልድዮችን አጠቃላይ 21 ፕሮጄክቶችን መርቀን ለአገልግሎት ክፍት አድርገናል፡፡

ከተማችንን ለማዘመን ከኮሪደር ልማት ስራዎቻችን ባሻገር የመንገድ መሰረተ ልማት ተደራሽነትን ለማረጋገጥ ልዩ ትኩረት ሰጥተን እየሰራ እንገኛለን፡፡ 

ዛሬ የተመረቁት እነዚህ የመንገድ መሰረተ ልማቶች ፦

ከአጉስታ- ወይራ መጋጠሚያ፣ቱሉዲምቱ ኮንዶሚኒያም መቃረቢያ፣
ከቃሊቲ ቀለበት መንገድ አደባባይ - በአቃቂ ድልድይ-ቱሉ ዲምቱ አደባባይ፣
ከቃሊቲ ቀለበት መንገድ አደባባይ ቡልቡላ-ቂሊንጦ 2ኛ ቀለበት መንገድ አደባባይ፣
 የለቡ አደባባይ ማሻሻያ ፕሮጀክት፣
ከአፍሪካ ህንፃ- ጀሞ መስታዎት ፋብሪካ፣
ከቂርቆስ ማርገጃ - ቡልጋሪያ፣
 ከቤላ -ፈረንሣይ ፓርክ - ፈረንሣይ አቦ ቤተክርስቲያን፣
ከናሰዉ ሪል ስቴት አርሴማ ቀለበት መንገድ እና ዮናስ ሆቴል ኬብሮን ፋርማሲ አስፋልት መንገዶች ናቸው፡፡

  ፈጣሪ  ኢትዮጵያን እና ህዝቧቿን ይባርክ

           ከንቲባ አዳነች አቤቤ

ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች
  https://linktr.ee/addisababacommunication


Comments

ምንም አልተገኘም.

አስተያየቶችዎን ይተዉት.