.png)
#የጠሚሩምላሾች #PMOEthiopia
የመሃሉ ዘመን ወጥመድን በተመለከተ
የመሃል ዘመን ማለት በሽግግሩ ማጠናቀቂያና በጸናው ስርዓት መጀመሪያ ላይ ማለት ነው። ስድስት ዓመታት የፖለቲካ ሪፎርም አደረግን የሰፈር ፓርቲ አጥፍተን ብልጽግናን ፈጠርን፡ በየሰፈሩ የነበረን ፓርቲ አምጥተን ብልጽግናን መፍጠር በራሱ ትልቅ እምርታ ነው። እኛ ያደረግነውን እኮ ብዙዎቹ አልቻሉም ገና በማህበራዊ ድረ ገጽ ውስጥ ነው ያሉት። ከተቋማት ሪፎርም ጀምሮ የተሟላ ኢኮኖሚ ሪፎርም ስላደረግን ነው መሃል ያልነው። ይሄ ማለት ሽግግሩም መቶ በመቶ አልጠፋም የጸናውም መቶ በመቶ አልጀመረም። መሃል ላይ ነው ያለነው። ያኛው እያለቀ ይህኛው እየጀመረ ማለት ነው። በዚህ ጊዜ ብዙ ድካሞች አሉ። የለውጥ ድካም የሚጀምረው መሃል ላይ ነው። መጀመሪያ ሁሉም ጉልበት አለው በኋላ ያለው ነገር የሚጨበጥ የሚነካ ይሆናል። ለምንድን ነው የመሃሉ ዘመን የሚያመጣብንን ፈተና እንጠንቀቅ ያልነው ብዙ ፈተና አይተናል። ብዙ ድል አግኝተናል፤ እኛ ባለፉት ዓመታት ኢትዮጵያ ውስጥ የሰራናቸው ስራዎች ላለፉት ሀምሳ እና ስልሳ ዓመታት አልተሰሩም ተጨባጭ ለውጥ አለ ኢትዮጵያ ውስጥ። ይህ ግን እንዳያኩራራን መድረስ የሚገባን ቦታ ሳንደርስ አንቆ እንዳያስቀረን አልቀን እንድንሰራ ፈተናን እንዳንለማመድ ድልን ደግሞ ማቀብና መጠበቅ እንድንችል ነው። መሃል ወደ ፊትም መስፈንጠር ያስችላል፤ ወደኋላም እንደገና ሊያንሸራትተን ይችላል ። ለዚህ ነው ነቅተን የመሃሉ እስረኛ እንዳንሆን ያልነው። ከዘመን ጋር የምንዘምን፣ ዘመንን የምንዋጅ፣ አብረን እንድናድግ፣ ባለንበት እንዳንቆም ካስፈለገ የመሃሉ ዘመን ፈተናን መገንዘብ ያስፈልጋል።
Comments
ምንም አልተገኘም.
አስተያየቶችዎን ይተዉት.