“ትውልድ በመምህራን ይቀረፃል ሀገር በትምህርት...

image description
- ውስጥ Current Affairs    0

“ትውልድ በመምህራን ይቀረፃል ሀገር በትምህርት ይበለፅጋል!” በሚል መሪ ቃል በየደረጃው ሲካሄድ የነበረው የመምህራን ውይይት የማጠቃለያ መድረክ አድርገናል::

መድረኩ ለሀገር ግንባታ መምህራን ያላቸውን ታላቅ ሚና በመረዳት በሀገራዊ ጉዳዮች የጋራ መግባባት ላይ ለመድረስ እንዲሁም ከመምህራን የሚነሱ ጥያቄዎችን እና ሃሳቦችን በማዳመጥ ተገቢውን ምላሽ ለመስጠት የተዘጋጀ ነው::

መምህራንና ቤተሰቦቻቸው በነፃ የሚታከሙበት ሆስፒታል ግንባታን ጨምሮ ሌሎች መምህራኑ ያነሷቸውን ሃሳቦች እና ጥያቄዎች ደረጃ በደረጃ በአጭር፣ በመካከለኛ እና በረጅም ጊዜ በዘላቂነት ለመፍታት ተግባብተናል::

መምህራኖች የትውልድ ግንባታ ስራችንን በመገንዘብ እዉቅና የሰጡ ሲሆን እኛም ላበረከቱት  አስተዋፆኦ ሁሉ ከልብ አመስግነናል::

ፈጣሪ ኢትዮጵያን እና ህዝቦቿን ይባርክ!

ከንቲባ አዳነች አቤቤ


Comments

ምንም አልተገኘም.

አስተያየቶችዎን ይተዉት.