ኢ/ር ወንድሙ ሲታ በም/ከንቲባ ማአረግ አዲስ አ...

image description
- ውስጥ Current Affairs    0

ኢ/ር ወንድሙ ሲታ በም/ከንቲባ ማአረግ አዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ዋና ስራ አስኪያጅ

👉የከተማዋን የፍሳሽ ማስጋጃ ስርዓት የማዘመንና በአዲስ መልከ የመገንባት ስራ በስፋት እየተከነወነ ይገኛል፡፡

👉የአደጋ ስጋት ተጋላጭነትን ለመቀነስ በልዩ በትኩረት አካባቢዎችን በመለየት እየሰራ ነው፡፡

👉የቆሻሻ አስተዳደር ስርዓት ላይ ያመጣነው ለውጥና ያስገኘነው ውጤት በከተማችን ገፅታ ላይ ግልፅ ለውጥ እያመጣ ነው::

👉ቆሻሻን ወደ ኢነርጂ ከመቀየር አንፃር አሁንም የሚቀሩን ስራዎች አሉ፤  የከተማዋን ፅዳት አረጋግጠን ቆሻሻን ወደ ኢነርጂ መቀየር ላይ በትኩረት መስራት ይኖርብናል።

👉ከውሃ ፍትሃዊ ስርጭት አንፃር 377,000 ሜ.ኪዩብ ውሃ የማምረት አቅም በማጎልበት ተደራሽነታችንን ለማሰደግ የተሰራ ሲሆን በቀጣይ 100,000 ሜ.ኪዩብ ተጨማሪ የውሃ አቅርቦት አቅም ለመፍጠር በትኩረት እየሰራን ነው::

👉የመብራት መቆራረጥ ችግር መንስኤዎች በነባር መንደሮች ያለውን አሮጌ መሰረተ ልማት    ጋር የተገናኘ በመሆኑ በቀጣይ የመብራት ሃይል አቅርቦት መሰረተ ልማትን በአዲስ መልክ ለመገንባት በማስተርፕላኑ  ውስጥ ማስገባት በዘላቂነት ለመፍታት ያግዘናል ፡፡

👉የኮሪደር ልማት ሰራችን ይህንን የመሰረተ ልማት ችግር ለመቅረፍ በሚያስችል መልኩ እየተሰራ ይገኛል፡፡


Comments

ምንም አልተገኘም.

አስተያየቶችዎን ይተዉት.